Telegram Group & Telegram Channel
ሰቀሉህ !!!

አንተስ ሁሉን ስታውቅልን ለራስህ አላውቅ ብለህ በዳይህን እንዴት ትፈጥራለህ ? እኛን የሚያዋድደን አለማወቅ ፣ አለመተዋወቅ ነው ። አንተ ብቻ አውቀህ ትወደናለህ ። ሰቀሉህ መልኬ ያልካቸው ፣ ዝቅ ብለህ ከአፈር ያነሣሃቸው ፣ ሬሳቸውን በአፍህ እስትንፋስ ሕያው ያደረግህላቸው ፣ ሚሊየን ጊዜ አድርገህላቸው አንድ ምስጋና የማያውቁ እነዚያ የአዳም ዘሮች ሰቀሉህ ። አንተ ለሁሉ እንደ ተሰቀልህ ፣ አንተን ሁሉ ሰቀለህ ። ከነጻነት ጋር የፈጠርሃቸው እነርሱ የግርግሪት አሰሩህ ። ካንተ በርባንን መረጡ ፣ አልጋ ስትሰጣቸው አመድ ላይ ተንከባለሉ ። የማይፈርድ ችሎት ፣ እውነትን የማይሻ ሸንጎ አቋቁመው ፣ ፍርድ ቤት አድርሰነዋል ለማለት አደባባይ አቆሙህ ። ስለመግደልህ ሳይሆን ስለመፈወስህ ሞት በየኑብህ ። አንተም አርፈህ አልቀመጥ ፣ ሲጠሉህ አልጠላችሁም ብለህ ይኸው ሰቀሉህ !

የሚደበድባትን ባል ያፈቅረኛል የምትል ሚስት ፣ የሚለመጥጠውን ንጉሥ ቆራጥ መሪ የሚል ሕዝብ ባለበት ዓለም በትዕግሥትህ ምክንያት ሰቀሉህ ። ገራፊ የለመደው ወገን የምትገረፍለትን አንተን መቀበል አቃተው ፣ ዛሬም አስመሳዮች ጌታን ተቀበልን እያሉ ራሳቸውን በመቀበል ፣ የተሰቀልከውን ሳይሆን ምቾታቸውን በማሳደድ ይሰቅሉሃል ። አንተም እንቢ አልክ ሁለት ሺህ ዓመት ልብ አልገዛም ብለህ በየጓዳው ፣ በየምርጫው ይሰቅሉሃል ። አይሁድ ስለሰቀሉህ የሚያለቅሱ ደጋግመው በክፋታቸው የሚሰቅሉህ ግብዞች ባሉበት ዓለም አንተ ተሰቀልህ ። ለሰቀሉህ ተሰቀልህላቸው ። ለገደሉህ ሞታቸውን ወሰድህላቸው ። የታመመ ቢታመሙለት አይድንም ። የሞተ ቢሞቱለት ቀና አይልም ። አንተ ግን በመገረፍህ ቍስል የምታድን ፣ በሞትህ ሕይወት የምትሰጥ ነህ ። ይገርማል ሥጋዬን ብሉ ስላልህ ላይበሉህ ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሰቀሉኝ አላልህም ፣ ተሰቀልሁላቸው አልህ አንጂ ።

ባንተ ምክንያት ከስንቱ ልጣላ ። ከዙፋን በረትን ፣ ከሰማይ አፈርን መርጠህ በመምጣትህ በር ዘጉብኝ አትበል ። ፍጥረተ ዓለሙን አንዱን በእንጀራ ፣ አንዱን በምስጋና እያጠገብህ የምትኖረው የብላቴናዋን የድንግልን ወተት የለመንከው እኮ ምን ቸግሮህ ነው ! ጠላት የሚፋንንብኝ ባልችል ፣ ድህነት የሚጎስመኝ ቢሳነኝ ነው ። አንተ ግን ወዶ ገብ ድሀ ለምን ሆንህ ! እኮ ከመውደድ አያርፍም ፣ በመጥላት ይራቀን ብለው ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሞኝ ሆነህ ሳይሆን አፍቅረህ ፣ መላ አጥተህ ሳይሆን መለኛ ሆነህ ሰቀሉህ ! የባለጠጋው ልጅ ድህነትን ፈቅደህ ተቀበልከው ። ሰውን ለማዳን ሰው ልሁን ብለህ መጣህ ። ሰው ሳይሆኑ ሰውን ለማዳን የሚነሡ ብዙዎች አሉና ልታስተምራቸው ፣ ለሰው ከመሰቀል በፊት ሰው መሆን ይቀድማል ልትላቸው ሰው ሆነህ መጣህ ። የክፋት ብርድ ልብሳቸውን በትምህርት ገፈፍካቸውና ተው ስልህ ይኸው ሰቀሉህ !

የአብ ልጅ ፣ የድንግል ልጅ ያንተ ሞት ግሩም ነው ። በአንድ ዓይን እያስለቀሰ ፣ በአንድ ዓይን የሚያስቅ ነው ። በሚኖርበት ዕድሜ የሚሞቱት ቀዘባዎች ፣ መለሎዎች ፣ ሙናዎች በኀዘን ሰብረውን እንዳይኖሩ አንተ በሠላሳ ሦስት ዓመትህ ሰቀሉህ ። ከሞቱ ያሟሟቱ እያሉ በአደባባይ ለሚወድቁት የሚያለቅሱ አሉና አንተ በአደባባይ በመሰቀል ተጽናኑ አልህ ። ሟች ሁሉ ልብስ አይገፉትም ፣ ለመገነዣም አዲስ ልብስ ይሰፋለታል ። አንተን ግን ልብስህን ገፍፈው ሰቀሉህ ። እነርሱ እኮ ምን ያድርጉ ! ብቻቸውን በር ዘግተው የሚበሉ ናቸው ፤ አንተ አምስት ሺህ ሰው ትመግባለህ ። ሐኪም ቤቱን ልታራቁት በነጻ ትፈውሳለህ ። ባንተ ምክንያት ምግብ ቤቶች ፣ ሸክላ የሚያበሉ ጨካኝ ነጋዴዎች ገቢያቸው ቀነሰ ። አዎ ሰቀሉህ ! እንዲሰቅሉህ ስለፈቀድህላቸው ሰቀሉህ ። መስቀል የቻሉ ትንሣኤህን ማገድ አልቻሉም ።

ዛሬም ድሀ እየበደሉ ፣ ፍርድ እያጓደሉ ፣ ለወንድም መርዝ እየበጠበጡ ይሰቅሉሃል ። አንተ ስለሁሉ በሞትህበት ዓለም ሁሉ አንድ ሰውን ተባብረው ይሰቅሉታል ፣ በድንጋይ ይወግሩታል ። የደቦ ፍርድ ይሰጡታል ። ኦ ምንድነው የምትፈልገው ከእኔ ፣ እስቲ ተወኝ ! እኮ ብያለሁ ዛሬም ሰቀሉህ !!!

የእናትህ ዘመዶች ሰቀሉህ ። እኮ እርሷስ ላንተ ታልቅስ ወይስ ዘመድ ትቀየም ! ቅያሜው እንዲቀር በመስቀል ላይ ይቅር አልህ ! ልቅሶው እንዲሻር ከሞት ተነሣህ ። አንተ ብሩህ ኮከብ ፣ ላያጠፉህ የመቱህ አማኑኤል ሆይ ብቻህን አትነሣ ፣ እኛንም ይዘህ ተነሣ ! ማር ኢየሱስ ጣፋጭ ነህ ! ማር ኢየሱስ መሐሪ ነህ ! የአፍሪካ ቀንድ ላይ ተቀምጠን ጦርነት አላጣ ያለን ሕዝቦችህን የተሰቀልኸው እባክህ ሰላም ስጠን !



ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3928
Create:
Last Update:

ሰቀሉህ !!!

አንተስ ሁሉን ስታውቅልን ለራስህ አላውቅ ብለህ በዳይህን እንዴት ትፈጥራለህ ? እኛን የሚያዋድደን አለማወቅ ፣ አለመተዋወቅ ነው ። አንተ ብቻ አውቀህ ትወደናለህ ። ሰቀሉህ መልኬ ያልካቸው ፣ ዝቅ ብለህ ከአፈር ያነሣሃቸው ፣ ሬሳቸውን በአፍህ እስትንፋስ ሕያው ያደረግህላቸው ፣ ሚሊየን ጊዜ አድርገህላቸው አንድ ምስጋና የማያውቁ እነዚያ የአዳም ዘሮች ሰቀሉህ ። አንተ ለሁሉ እንደ ተሰቀልህ ፣ አንተን ሁሉ ሰቀለህ ። ከነጻነት ጋር የፈጠርሃቸው እነርሱ የግርግሪት አሰሩህ ። ካንተ በርባንን መረጡ ፣ አልጋ ስትሰጣቸው አመድ ላይ ተንከባለሉ ። የማይፈርድ ችሎት ፣ እውነትን የማይሻ ሸንጎ አቋቁመው ፣ ፍርድ ቤት አድርሰነዋል ለማለት አደባባይ አቆሙህ ። ስለመግደልህ ሳይሆን ስለመፈወስህ ሞት በየኑብህ ። አንተም አርፈህ አልቀመጥ ፣ ሲጠሉህ አልጠላችሁም ብለህ ይኸው ሰቀሉህ !

የሚደበድባትን ባል ያፈቅረኛል የምትል ሚስት ፣ የሚለመጥጠውን ንጉሥ ቆራጥ መሪ የሚል ሕዝብ ባለበት ዓለም በትዕግሥትህ ምክንያት ሰቀሉህ ። ገራፊ የለመደው ወገን የምትገረፍለትን አንተን መቀበል አቃተው ፣ ዛሬም አስመሳዮች ጌታን ተቀበልን እያሉ ራሳቸውን በመቀበል ፣ የተሰቀልከውን ሳይሆን ምቾታቸውን በማሳደድ ይሰቅሉሃል ። አንተም እንቢ አልክ ሁለት ሺህ ዓመት ልብ አልገዛም ብለህ በየጓዳው ፣ በየምርጫው ይሰቅሉሃል ። አይሁድ ስለሰቀሉህ የሚያለቅሱ ደጋግመው በክፋታቸው የሚሰቅሉህ ግብዞች ባሉበት ዓለም አንተ ተሰቀልህ ። ለሰቀሉህ ተሰቀልህላቸው ። ለገደሉህ ሞታቸውን ወሰድህላቸው ። የታመመ ቢታመሙለት አይድንም ። የሞተ ቢሞቱለት ቀና አይልም ። አንተ ግን በመገረፍህ ቍስል የምታድን ፣ በሞትህ ሕይወት የምትሰጥ ነህ ። ይገርማል ሥጋዬን ብሉ ስላልህ ላይበሉህ ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሰቀሉኝ አላልህም ፣ ተሰቀልሁላቸው አልህ አንጂ ።

ባንተ ምክንያት ከስንቱ ልጣላ ። ከዙፋን በረትን ፣ ከሰማይ አፈርን መርጠህ በመምጣትህ በር ዘጉብኝ አትበል ። ፍጥረተ ዓለሙን አንዱን በእንጀራ ፣ አንዱን በምስጋና እያጠገብህ የምትኖረው የብላቴናዋን የድንግልን ወተት የለመንከው እኮ ምን ቸግሮህ ነው ! ጠላት የሚፋንንብኝ ባልችል ፣ ድህነት የሚጎስመኝ ቢሳነኝ ነው ። አንተ ግን ወዶ ገብ ድሀ ለምን ሆንህ ! እኮ ከመውደድ አያርፍም ፣ በመጥላት ይራቀን ብለው ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሞኝ ሆነህ ሳይሆን አፍቅረህ ፣ መላ አጥተህ ሳይሆን መለኛ ሆነህ ሰቀሉህ ! የባለጠጋው ልጅ ድህነትን ፈቅደህ ተቀበልከው ። ሰውን ለማዳን ሰው ልሁን ብለህ መጣህ ። ሰው ሳይሆኑ ሰውን ለማዳን የሚነሡ ብዙዎች አሉና ልታስተምራቸው ፣ ለሰው ከመሰቀል በፊት ሰው መሆን ይቀድማል ልትላቸው ሰው ሆነህ መጣህ ። የክፋት ብርድ ልብሳቸውን በትምህርት ገፈፍካቸውና ተው ስልህ ይኸው ሰቀሉህ !

የአብ ልጅ ፣ የድንግል ልጅ ያንተ ሞት ግሩም ነው ። በአንድ ዓይን እያስለቀሰ ፣ በአንድ ዓይን የሚያስቅ ነው ። በሚኖርበት ዕድሜ የሚሞቱት ቀዘባዎች ፣ መለሎዎች ፣ ሙናዎች በኀዘን ሰብረውን እንዳይኖሩ አንተ በሠላሳ ሦስት ዓመትህ ሰቀሉህ ። ከሞቱ ያሟሟቱ እያሉ በአደባባይ ለሚወድቁት የሚያለቅሱ አሉና አንተ በአደባባይ በመሰቀል ተጽናኑ አልህ ። ሟች ሁሉ ልብስ አይገፉትም ፣ ለመገነዣም አዲስ ልብስ ይሰፋለታል ። አንተን ግን ልብስህን ገፍፈው ሰቀሉህ ። እነርሱ እኮ ምን ያድርጉ ! ብቻቸውን በር ዘግተው የሚበሉ ናቸው ፤ አንተ አምስት ሺህ ሰው ትመግባለህ ። ሐኪም ቤቱን ልታራቁት በነጻ ትፈውሳለህ ። ባንተ ምክንያት ምግብ ቤቶች ፣ ሸክላ የሚያበሉ ጨካኝ ነጋዴዎች ገቢያቸው ቀነሰ ። አዎ ሰቀሉህ ! እንዲሰቅሉህ ስለፈቀድህላቸው ሰቀሉህ ። መስቀል የቻሉ ትንሣኤህን ማገድ አልቻሉም ።

ዛሬም ድሀ እየበደሉ ፣ ፍርድ እያጓደሉ ፣ ለወንድም መርዝ እየበጠበጡ ይሰቅሉሃል ። አንተ ስለሁሉ በሞትህበት ዓለም ሁሉ አንድ ሰውን ተባብረው ይሰቅሉታል ፣ በድንጋይ ይወግሩታል ። የደቦ ፍርድ ይሰጡታል ። ኦ ምንድነው የምትፈልገው ከእኔ ፣ እስቲ ተወኝ ! እኮ ብያለሁ ዛሬም ሰቀሉህ !!!

የእናትህ ዘመዶች ሰቀሉህ ። እኮ እርሷስ ላንተ ታልቅስ ወይስ ዘመድ ትቀየም ! ቅያሜው እንዲቀር በመስቀል ላይ ይቅር አልህ ! ልቅሶው እንዲሻር ከሞት ተነሣህ ። አንተ ብሩህ ኮከብ ፣ ላያጠፉህ የመቱህ አማኑኤል ሆይ ብቻህን አትነሣ ፣ እኛንም ይዘህ ተነሣ ! ማር ኢየሱስ ጣፋጭ ነህ ! ማር ኢየሱስ መሐሪ ነህ ! የአፍሪካ ቀንድ ላይ ተቀምጠን ጦርነት አላጣ ያለን ሕዝቦችህን የተሰቀልኸው እባክህ ሰላም ስጠን !



ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3928

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram hopes to raise $1bn with a convertible bond private placement

The super secure UAE-based Telegram messenger service, developed by Russian-born software icon Pavel Durov, is looking to raise $1bn through a bond placement to a limited number of investors from Russia, Europe, Asia and the Middle East, the Kommersant daily reported citing unnamed sources on February 18, 2021.The issue reportedly comprises exchange bonds that could be converted into equity in the messaging service that is currently 100% owned by Durov and his brother Nikolai.Kommersant reports that the price of the conversion would be at a 10% discount to a potential IPO should it happen within five years.The minimum bond placement is said to be set at $50mn, but could be lowered to $10mn. Five-year bonds could carry an annual coupon of 7-8%.

Export WhatsApp stickers to Telegram on Android

From the Files app, scroll down to Internal storage, and tap on WhatsApp. Once you’re there, go to Media and then WhatsApp Stickers. Don’t be surprised if you find a large number of files in that folder—it holds your personal collection of stickers and every one you’ve ever received. Even the bad ones.Tap the three dots in the top right corner of your screen to Select all. If you want to trim the fat and grab only the best of the best, this is the perfect time to do so: choose the ones you want to export by long-pressing one file to activate selection mode, and then tapping on the rest. Once you’re done, hit the Share button (that “less than”-like symbol at the top of your screen). If you have a big collection—more than 500 stickers, for example—it’s possible that nothing will happen when you tap the Share button. Be patient—your phone’s just struggling with a heavy load.On the menu that pops from the bottom of the screen, choose Telegram, and then select the chat named Saved messages. This is a chat only you can see, and it will serve as your sticker bank. Unlike WhatsApp, Telegram doesn’t store your favorite stickers in a quick-access reservoir right beside the typing field, but you’ll be able to snatch them out of your Saved messages chat and forward them to any of your Telegram contacts. This also means you won’t have a quick way to save incoming stickers like you did on WhatsApp, so you’ll have to forward them from one chat to the other.

Nolawi ኖላዊ from cn


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA